Thursday, 16 May 2013

biruk

እንመዘገባለን፣ እንደ አዲስም እንታወቃለን


ሰሞኑን የፌድራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሃይማኖት ተቋማትን ለመመዝገብ የወጣ ረቂቅ መመሪያ› የሚል ወረቀት አስተያየት ይሰጥበት ዘንድ ለእምነት ተቋማት አሠራጭቷል፡፡ ይህ መመርያ የያዛቸውን ጉዳዮች እያንዳንዳቸውን እየነጠሉ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም ወደፊት የምናደርገው ይሆናል፡፡ ለአሁኑ ግን መመሪያውን ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ነባራዊ፣ ሉዓላዊና መንፈሳዊ ጠባያት ጋር በማዛመድ ብቻ እንመለከተዋለን፡፡
1.       መመሪያው የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዩ ሁኔታ ከግምት ያላስገባ ነው
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 2000 ዓመታት በምድሪቱ ላይ የኖረች፣ የሰበከች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ ክፉውንም ሆነ ደጉንም እኩል የቀመሰች፣ እንዲያውም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመሆንዋ ብቻ ልዩ ጉዳት የደረሰባትም ናት፡፡ በጣልያን ወረራ ጊዜ የተሠውትን ጳጳሳትና መነኮሳት ማሰቡ ብቻ ለዚህ የቅርብ ምሳሌ ነው፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ሂደት ውስጥ በሀገሪቱ ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ውስጥ ልዩ የሆነና የማይተካ ሚና ተጫውታለች፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ተመሥርታ ሀገሪቱንም መሥርታለች፡፡
ይህንን ሁሉ ዘንግቶ በ2005 ዓም ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ አዲስ ተመዝገቢ፣ እንደ አዲስ ፈቃድ አውጭ፣ እንደ አዲስ ደንብና መመሪያሽን አምጭ ማለት እጅግ አሳዛኝም አስገራሚም ነገር ነው፡፡ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም ራሱ ከፈለገ መረጃ ሰብስቦ መመዝገብና ማወቅ ነበረበት እንጂ ሰነድ አምጭ፣ ደንብ አስገቢ፣ ፈቃድ አውጭና ልወቅሽ ማለት አልነበረበትም፡፡

Tuesday, April 23, 2013

አማርኛ ከሠላሳ ዓመት በኋላ



 
የዛሬ ሠላሳ ዓመት በ2035 ዓም በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች መካከል የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ውድድር ይደረጋል፡፡ በውድድሩም ከዚህ በታች የማቀርብላችሁ ወግ ‹እኔና ትምህርት ቤቴ› በሚል ርእስ ተወዳድሮ አንደኛ ይወጣል፡፡
ይህ ኦፖርቹኒቲ ስለ ተሰጠኝ ታንክዩ፡፡ አቦ ይመቻችሁ፡፡ ሀገራችን ኢቶጲያ ሚራክልየስ ሀገር ናት፡፡ አይ ሚን ነፍስ ነገር ናት፡፡ ይህንን ስል ግን ሙድ እንዳትይዙብኝ፡፡ እዚህ ሀገር ብዙ ነገር ነፍ ነው ማለቴ ነው፡፡ ዋተር ነፍ ነው፣ ኦፕን ኤይር ነፍ ነው፣ ሰን ሴትና ሰን ራይዝ ነፍ ነው፡፡ ማዩንቴይን ነፍ ነው፤ የሚደብረው ነገር ሮዶቹና ቪሌጆቹ ምልክት የላቸውም፡፡ ፎር ኤግዛምፕል የኛን ቤት ለሰው ስንነግር ‹ኒር እንትና ጫት ቤት› ነው የምንለው፡፡ ቢኮዝ እዚህ ሀገር ጫት ቤት ነፍ ነዋ፡፡ አት ዚስ ፖይንት ኤክስፕሌይን ማድረግ አለብኝ፡፡ የአያቴን ካፕ ቦርድ ስሾፍ አዲስ ዘመን የሚባል አንድ የድሮ ኒውስ ፔፐር አገኘሁና፡፡ ኮለመኑ ላይ ‹በምግብ ራስን መቻል› የሚል ነገር ሾፍኩ፡፡ ነገሩ ክሊር አልሆነልኝም ነበር፡፡ ዋት ኢዝ ‹ራስን መቻል›? ራስ ማለት ‹ሄድ› አይለደም እንዴ? መቻልስ ምንድን ነው? አንዱን ፍሬንዴን አስክ ሳደርገው ‹መቻል የሚባል ኦልድ ውሻ ጎረቤታችን አለ› አለኝ፡፡ ስለዚህ ራስን መቻል ሚን ‹የመቻል ራስ› ማለት ነው፡፡ 

Tuesday, April 16, 2013

የዓመቱ ‹በጎ ሰው›

የዳንኤል ዕይታዎች ‹የዓመቱ በጎ ሰው› የምርጫ ኮሚቴ ሰባት አባላት ነበሩት፡፡ እነዚህ አባላት ከተለያዩ ሞያዎችና አካባቢዎች የመጡ ሲሆን በ‹የዳንኤል ዕይታዎች› አማካኝነት ለአንድ ወር ያህል አንባብያን ‹በጎ ሰው› የሚሉትን እንዲጠቁሙ ዕድል ተሰጥቶ ነበር፡፡ በዚህም መሠረት በ159 ጠቋሚዎች 70 ግለሰቦችና ሰባት ተቋማት ተጠቁመዋል፡፡
እነዚህን 70 ኢትዮጵያውያንና ሰባት ተቋማትን አመዛዝነው አሥር ምርጦችን እንዲሰይሙ በተለያዩ ክልሎችና ሞያዎች ለሚገኙ እርስ በርሳቸውም ለማይተዋወቁ 9 ሰዎች ተሰጠ፡፡ በዚህም መሠረት ከጠቋሚዎችና ከመራጮች የተሻሉ ድምፆችን ያገኙ አሥራ ሰባት ሰዎች ተመረጡ፡፡
እነርሱም